ከ2008 እ.ኤ.አ ጀምሮ
ስለ እኛ
ታሪካችንን

ስለ እኛ የበለጠ
ድርጅቱ የተመሠረተበት ዓላማ በኢትዮጵያ ውስጥ በሲሚንቶ አቅርቦት እና ፍላጎት መካከል ያለውን ክፍተት መሙላት እና በአገሪቱ ውስጥ የሚካሄደውን የመሠረተ-ልማት እና የቤቶች ግንባታ ሂደት በማፈጠን እገዛ ለማድረግ ጥራት ያለውን ሲሚንቶ እና ሌሎች የግንባታ ግብዓቶችን ማቅረብ ነው። በአሁኑ ወቅት ፋብሪካው ኦፒሲ (ኦሪዲናሪ ፖርትላንድ ሲሜንት) እና ፒፒሲ (ፖዞላና ፖርትላንድ ሲሜንት) የተባሉ ሁለት ዓይነት የሲሚንቶ ምርቶችን ያመርታል። በደንበኞች ፍላጎት መሠረት ተመርተው የደንበኞችን ልዩ ፍላጎቶች ማሟላት የሚችሉ አዳዲስ ምርቶችን ወደገበያው የማስገባት ዕቅዶችም አሉት። ፋብሪካው በቀን 3000 ቶን ክሊንከር እና 4500 ቶን ፒፒሲ ሲሚንቶ የማምረት አቅም አለው። ሐበሻ ሲሚንቶ የደንበኞቹን እና የባለአክሲዮኖችን ፍላጎት በማሟላት የሚያምን ሲሆን እንቅስቃሴዎቹ ሁሉ ያነጣጠሩት እነዚህን ዓላማዎች ከግብ በማድረስ ላይ ነው። ድርጅቱ ለ941 ኢትዮጵያዊ ሠራተኞች የሥራ ዕድል የፈጠረ ሲሆን እነዚህም የከፍተኛ አመራርነትን ጨምሮ በተለያዩ የስራ መስኮች ተሠማርተው ይገኛሉ።
ራእይ
በዘላቂ ልማት ላይ በማተኮር እና የባለድርሻ አካላትን ፍላጎት ያማከለ በኢትዮጵያ ተቀዳሚ ምርጫ የግንባታ ግብዓቶች አምራችና አሠሪ/ ቀጣሪ ድርጅት ለመሆን
ዋና እሴቶች
ተልዕኮ


